የፀረ-ሙስና ዐቃቤ ሕግ መምሪያ በፌደራሉ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሥር ከተደራጁት ዓላማ አስፈፃሚ መምሪያዎች አንዱ ነው፡፡ መምሪያው የተጣለበትን ተግባርና ኃላፊነት ለመወጣት እንዲያስችለው በቂ ባለሙያዎች እንዲኖሩት ሆኖ የተቋቋመ ነው፡፡  

ይሁንና በአሁኑ ጊዜ የተወሰኑ ዐቃቢያነ ሕጐች ብቻ ያሉት በመሆኑ የሰው ኃይል እጥረት የሚታይበት ነው፡፡ 

መምሪያው የተደራጀበት ዋና ዓላማ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ የተጣራባቸውን ፋይሎች መርምሮ ወንጀል ፈፃሚ ተጠርጣሪዎችን ስልጣን ባለው ፍ/ቤት ክስ መስርቶ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ እና በሙስና ወንጀል የተገኘን ንብረት በማሳገድ እና እንዲወርስ በማድረግ በፀረ-ሙስና ትግሉ ጉልህ የሙስና ወንጀል የመከላከል ተግባርን ውጤታማ ማድረግ ነው፡፡ 

ይህን ዓላማ ተፈፃሚ ለማድረግ መምሪያው ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል ዋና ዋናዎቹ፡-

·        በወንጀል ሕግ እና በሌሎች ሕጐች የሙስና ወንጀሎች ፈፅመዋል ተብለው በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ምርመራ የተጣራባቸው የምርመራ መዛግብት ሲደርሱት በማጥናትና በመመርመር በቂ ማስረጃ ያልተገኘባቸውን ክስ ሊቀርብባቸው አይገባም የሚል ውሣኔ በመስጠት ይዘጋል፣ ተጨማሪ ምርመራ የሚያስፈልጋቸውን የምርመራ መዝገቦች ተጨማሪ ምርመራ ተደርጐ ምርመራው ተጠናክሮ ውጤቱ እንዲቀርብለት ለመርማሪው አካል ይመልሳል፣ ክስ ለመመስረት የሚያስችል በቂ ማስረጃ በተሰባሰበባቸው የሙስና ወንጀል ምርመራ መዝገቦች ላይ የወንጀል ክስ በፍ/ቤት መስርቶ ተገቢውን በመፈፀም የመፋረድ፣

·        በሙስና ወንጀል ድርጊት ከተገኘ ንብረት ጋር በተያያዘ በምርመራ ላይ ያሉ ሰዎች ሀብት በፍ/ቤት ትዕዛዝ እንዳይንቀሳቀስ የማሳገድ፣

·        በሙስና ወንጀል የተገኘ ለመሆኑ የተረጋገጠን ማንኛውንም ንብረት ወይም ሀብት በፍ/ቤት ትዕዛዝ እንዲወረስና በሀራጅ ተሸጦ ወይም ሳይሸጥ ለመንግሥት ገቢ እንዲሆን የማድረግና

·        ስለመመርመርና ስለመክሰስ በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነሥርዓትና በሌሎች ሕጐች ለዐቃቤ ሕግ በተሰጠ ሥልጣን መሠረት ኮሚሽኑን በሚመለከቱ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ላይ ተገቢውን የመፈፀም ተግባራትን ያከናውናል፡፡ 

የፀረ-ሙስና  ዐቃቤ  ሕግ መምሪያ ከሌሎች የፍትህ አካላት ጋር ያለው ግንኙነት

ከኮሚሽኑ ምርመራ መምሪያ እና ከሌሎች የምርመራ አካላት ጋር

መምሪያው ግንኙነቱ በግንባር ቀደምትነት የተመሠረተው በኮሚሽኑ ሥር ከተደራጀው የምርመራ መምሪያ ጋር ሲሆን ይህ መምሪያ ከዐቃቤ ሕግ መምሪያ ጋር ያለው ግንኙነት የተመሠረተው ራሱ ባሉት መርማሪዎች አማካኝነት በሚያከናውናቸው የምርመራ ተግባራት ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ማለትም በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ መምሪያ፣ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ መምሪያዎች እና በክልል መንግሥታት ፖሊስ የምርመራ መምሪያ ምርመራቸው የተጠናቀቁ መዛግብት ለዐቃቤ ሕግ መምሪያ የሚደርሱት በኮሚሽኑ ምርመራ መምሪያ በኩል በመሆኑ ሁለቱ የኮሚሽኑ መምሪያዎች የጠበቀ የዕለት ተዕለት የሥራ ግንኙነት አላቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ተጠርጣሪዎችን በመያዝ፣ ለምስክሮች መጥሪያ በማድረስ እንዲሁም የሚታገዱ ንብረቶችን በማጥናት በኩል የሚደረገው የሥራ ግንኙነት ሁለቱን በጋራ የሚያገናኙ ጉዳዮች ናቸው፡፡ 

ከፍርድ ቤቶች ጋር

የፀረ-ሙስና አቃቤ ሕግ መምሪያ ከምርመራ መምሪያ ቀጥሎ ከፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ከክልል  ጠቅላይ  ፍርድ ቤቶች ጋር ጠንካራ ግንኙነት አለው፡፡ የግንኙነቱም መሠረት መምሪያው በፍርድ ቤቶች የሚያስከፍታቸው የሙስና ወንጀል ክስ ፋይሎች ሲሆኑ ትክክለኛ ፍትህ ሳይዘገይ የሚሰጥበት ሁኔታ እንዲመቻች በጋራ ይሰራሉ፡፡ 

ከሌሎች የዐቃቤ ሕግ ተቋማት ጋር

የፀረ-ሙስና ዐቃቤ ሕግ መምሪያ በፌደራራሉ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሥር ከተደራራጀበት ከ1993 ዓ.. ጀምሮ ከሌሎች የዐቃቤ ሕግ ተቋማት ጋር የተመሠረተ ቀጥተኛ የሆነ የሥራራ ግንኙነት ባይኖርም አልፎ አልፎ ከኮሚሽኑ ሥልጣን ክልል ውጭ የሆኑ የምርመራራ መዛግብት ሲያጋጥሙ በመሸኛ መረጃ የሚለዋወጡበት አሠራራር የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም ግን ወደፊት የተሻሻለውን የኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 433/97 መሠረት በማድረግ የፌዴራራሉም ሆነ የክልል ዐቃቤ ሕግ ተቋማት እና የክልል ሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤያነ-ሕግ የፌዴራራሉን መንግሥት እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ሕግን ወክለው የፌዴራራሉን መንግሥት የሚመለከቱ የሙስና ወንጀሎችን ሲከሱና ሲከራራከሩ በብዙ መንገድ ቀጥተኛ ግንኙነት እንደሚኖር ይታመናል፡፡