የሙስና
ወንጀል
ምርመራ
መምሪያ
መምሪያው
በመንግሥት
መ/ቤቶች
ወይም
በመንግሥት
የልማት
ድርጅቶች
ወይም
የፌደራል
መንግሥቱ
ለክልሎች
ከሚሰጠው
ድጐማ
ጋር
በተያያዘ
በክልል
መ/ቤቶች
በወንጀል
ሕግ
እና
በሌሎች
ሕጐች
ውስጥ
የተመለከቱት
የሙስና
ወንጀሎች
በመንግሥት
ሠራተኞች
ወይም
ባለሥልጣኖች
ወይም
በሌሎች
ሰዎች
ስለመፈፀማቸው
ጥቆማ
ሲደርሰው
ወይም
በቂ
ጥርጣሬ
ሲኖረው
የመመርመር
ወይም እንዲመረመር
የማድረግ
ተግባርና
ኃላፊነት
አለው፡፡
ከዚህ
አንፃር
የመምሪያው
ዋና
ተግባር
የተጠረጠሩ
የሙስና
ወንጀሎችን
እና
የሥነምግባር
ጥሰቶችን
በማጣራት
ጥፋተኞች
ክስ
እንዲመሰረትባቸው
የምርመራውን
ውጤት
ለዐቃቤ
ሕግ
መምሪያ
ማስተላለፍ
ነው፡፡
በመሆኑም
መምሪያው
ከተለያዩ
የሕብረተሰቡ
ክፍሎች
የሚደርሱትንና
በሙስና
ወንጀል
እና
በሥነምግባር
መተላለፍ
ዙሪያ
የሚያተኩሩ
ጥቆማዎችን
በአካል፣
በስልክ
ወይም
በደብዳቤ
በፋክስ
እና
በኢሜል
አማካኝነት
በመቀበል
እንደችግሩ
ይዘትና
ስፋት
ጥቆማው
በቅደም
ተከተል
የሚደራጅበትንና
ለምርመራ
ዝግጁ
የሚሆንበትን
አሠራር
ተግባራዊ
ያደርጋል፡፡
ከዚህ
በተጨማሪ
መምሪያው
የተጠርጣሪዎች
ሀብት
በፍርድ
ቤት
አማካኝነት
እንዳይንቀሳቀስ
በማስወሰን
ተጠራጣሪዎቹ
ጥፋተኝነታቸው
ከተረጋገጠ
ፍርድ
ቤት
በሚወስነው
መሠረት
የታገደው
ንብረት
ለፍርድ
ማስፈፀሚያ
እንዲውል
ሊያደርግ
ይችላል፡፡
ከሙስና
ወንጀል
ምርመራ
መምሪያ
ባለሙያዎች
መካከል
አንድን
የተጠረጠረ
የሙስና
ወንጀል
ጉዳይ
እንዲመረምር
የተመደበ
ሠራተኛ
ለምርመራ
ሂደቱ
ጠቃሚነት
አለው
ተብሎ
እስከታመነበት
ድረስ
ከማንኛውም
ድርጅት
ወይም
ግለሰብ
መረጃ
የማግኘት
መብት
አለው፡፡
ከዚህ
መረዳት
የሚቻለው
ምርመራቸው
በሂደት
ላይ
የሚገኙ
ተጠርጣሪ
የሙስና
ወንጀሎችን
ጉዳይ
በተመለከተ
መረጃ
እንዲሰጥ
የሚጠየቅ
ማንኛውም
አካል
በተጠየቀው
ጉዳይ
ላይ
መረጃ
ለመስጠት
ትብብር
ሊያሳይ
የሚገባው
መሆኑን
ነው፡፡
የሙስና
ወንጀል
ምርመራ
መምሪያ
ዳይሬክተር
በሙስና
የተጠረጠረን
ግለሰብ
ወይም
ጉዳይ
በምርመራ
ላይ
የሚገኝን
ተጠርጣሪ
በቁጥጥር
ስር
እንዲውል
የሚያስገድድ
አሳማኝ
ምክንያት
ካለው
ከ48
ሰዓት
ላልበለጠ
ጊዜ
በቁጥጥር
ስር
እንዲውል
ትዕዛዝ
የመስጠት
ስልጣን
አለው፡፡
ይህም
ሲሆን
ጉዳዩን
በቅድሚያ
ለሥነ
ምግባርና
ለፀረ-ሙስና
ኮሚሽን
ኮሚሽነር
አሳውቆ
ስምምነት
ማግኘት
ይኖርበታል፡፡
በሌላ
ወገን
ደግሞ
ማንኛውም
የመንግሥት
ተቋምም
ሆነ
ግለሰብ
ከባድ
የሥነምግባር
መጣስን
ጨምሮ
የሙስና ወንጀል
ለመፈፀሙ
ጥርጣሬ
ሲኖረው
ጉዳዩን
ለኮሚሽኑ
እንዲጠቁም
ይጠበቃል፡፡
የተወሰኑ
የመምሪያው
ተግባራት
እንዳስፈላጊነቱ
በሚስጥር
የሚጠበቁ
ናቸው፡፡
ለምሳሌ
በአንድ
መንግሥታዊ
ተቋም
የሙስና
ወንጀል
ለመፈፀሙ
ጥቆማ
ለማቅረብ
ወደ
ኮሚሽኑ
የሚመጡ
የሕብረተሰብ
ክፍሎች
ማንነት
በሚስጥር
ሊጠበቅላቸው
ይገባል፡፡
በተጨማሪም
በጅምር
የምርመራ
ደረጃ
ላይ
የሚገኝ
ጉዳይ
በወንጀሉ
ተጠያቂ
አካላት
እንዳይጠፉና
ተፈላጊ
መረጃዎቹም
እንዳይሰወሩ
ለማድረግ
በሚስጥር
ተጠብቆ
መቆየቱ
ይታመናል፡፡
ሆኖም
ግን
የሙስና
ወንጀልን
የማጣራት
ሂደት
በሚስጢር
ተጠብቆ
የሚቆየው
ተጠርጣው
በቁጥጥር
ስር
እስኪውል
ድረስ
ብቻ
ነው፡፡
መምሪያው
በጥቆማ
የሚቀርቡለትን
የተጠረጠሩ
የሙስና
ወንጀሎች
ጉዳይ
አንዱን
ከሌላው
ሳያበላልጥ
ለሁሉም
እኩል
ትኩረት
ሰጥቶ
ምርመራ
ሥራውን
ያካሂዳል
ምክንያቱም
በጥቆማ
አቀራረብ
ላይ
ዝቅተኛ
የሙስና
ወንጀል
ጉዳይ
መስለው
የሚታዩ
ጉዳዮች
በምርመራ
ሂደት
ከፍተኛ
የሙስና
ወንጀል
ያካተቱ
ጉዳዮች
ሊሆኑ
ይችላሉ፡፡
በሌላ
ወገን
ማንኛውም
የሕብረተሰብ
ክፍል
በፀረ-ሙስና
ዘመቻው
ላይ
የሚያሳየው
ተሳትፎ
የተጠናከረ
እንዲሆን
ከተፈለገ
ሁሉም
ዜጋ
ለኮሚሽኑ
በጥቆማ
የሚያቀርባቸው
የሙስና
ጉዳዮች
ተገቢው
ትኩረት
ተሰጥቷቸው
መጣራት
ስለሚገባቸው
ነው፡፡
ይህም በአነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሙስና ወንጀሎች ሳይቀሩ በኮሚሽኑ ትኩረት ተሰጥቷቸው ተገቢው ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው መደረጉ ሙስናን ሊሸከም የማይችል
ሕብረተሰብ
ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት አስተዋፅኦ ስለሚኖረው የትኛውም የሙስና ወንጀል ከሕዝብ ዕይታ ተሰውሮ ብዙ እንዳይቆይ ያደርጋል፡፡