| |
|
የፌደራል
የሥነምግባር እና
የፀረ ሙስና ኮሚሽን
ምሥረታ እና
እንቅስቃሴዎቹ
1 መግቢያ 2
የሙስና
ትርጓሜና፣
መገለጫዎች፣ ታሪካዊ
አመጣጥ፣
ምክንያቶችና
የሚያስከትለው ውጤት
ከኢትዮጵያ ተጨባጭ
ሁኔታ አንፃር 2.5 ሙስና እንደተንሰራፋባቸው የሚታመኑ የአገልግሎት ዘርፎች
1. መግቢያ የኢትዮጵያ
መንግሥት የፌደራል
የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንን
በግንቦት ወር 1993 ዓ.ም
በማቋቋም ሙስናን
መታገል ከጀመረ
ስድስት አመታት
የተቆጠሩ ሲሆን
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ
የሥነምግባር
ትምህርትን
በማስፋት፣ ሙስናን
በመከላከል፣
በመመርመርና
ሙሰኞችን ለፍርድ
በማቅረብ ረገድ
አበረታች ውጤቶች
ተመዝግበዋል፡፡
ነገር ግን የአቅም
ውሱንነትን ጨምሮ
ሌሎች ችግሮች ኮሚሽኑ
በተፈለገው ደረጃ
እንዳይንቀሳቀስ
እንቅፋት ባይሆኑበት
ኖሮ ከዚህ የበለጠ
ውጤት ሊገኝ ይችል
እንደነበር
ይታመናል፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ
በቀጣዮቹ አመታት
ከዚህ የተሻለ
ለመሥራት ይችል ዘንድ በፀረ-ሙስና
ትግሉ ያገባናል
የሚሉ ወገኖች ሁሉ
በንቃት
የሚሳተፉበትን ሁኔታ
እያመቻቸ ይገኛል፡፡ ከዚህ ጐን ለጐን
የፀረ-ሙስና ትግሉን
በተመለከተ
የህብረተሰቡ ግንዛቤ
እንዲዳብር የግንዛቤ
ማስጨበጫ ኘሮግራሞች
በስፋት መካሄድ
እንዳለባቸው ግልጽ
ነው፡፡ ህብረተሰቡ በፀረ-ሙስና ትግሉ
በንቃት ይሳተፍ ዘንድ
ስለ ሙስና ጐጅነት፣
መገለጫዎች፣
መንስኤዎች፣
መከላከያ መንገዶቹ
ወዘተ ማወቅ
አለበት፡፡ ስለአገር
አቀፉ የፀረ-ሙስና
እንቅስቃሴም በቂ
ግንዛቤ ሊያገኝ
ይገባል፡፡ ኮሚሽኑም ከላይ
የተጠቀሰውን ጉዳይ
አስፈላጊነት
በመረዳት እየተካሄደ
ባለው የፀረ-ሙስና እንቅስቃሴ
ዙሪያ ግንዛቤ
የሚያስጨብጡ
ስትራቴጂዎችን ነድፎ
በመተግበር ላይ
ይገኛል፡፡ ከነዚህ ተግባራት አንዱ በአገር አቀፉ የፀረ-ሙስና እንቅስቃሴ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ የሚሰጡ የህትመት ውጤቶችን ማሳተምና ማሰራጨት ነው፡፡ ይህ ጽሑፍም ይህንኑ አላማ ለማሳካት ይረዳ ዘንድ የተዘጋጀ ነው፡፡ ጽሁፉ በፀረ-ሙስና ትግሉ እስከአሁን የተከናወኑ ተግባራትን፣ ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በተያያዘ የሙስናን አመጣጥና የሚያስከትለውን ቀውስ፣ ሙስናን በመዋጋት ረገድ የወደፊት አቅጣጫዎችንና ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን በተመለከተ ጠቃሚ መረጃዎችን እንደማካተቱ መጠን በዘርፉ ምርምር ለሚያካሂዱ አካላት፣ ለተማሪዎች እና መምህራንን ጨምሮ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በቂ ግንዛቤ ያስጨብጣል ብለን እናምናለን፡፡ 2 የሙስና ትርጓሜና፣ መገለጫዎች፣ ታሪካዊ አመጣጥ፣ ምክንያቶችና የሚያስከትለው ውጤት ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ አንፃርበኢትዮጵያ ሙስና
የሚለው ቃል አመጣጡ
ከግዕዝ ነው፡፡ ይህ
ቃል «ጥፋት
እና ብልሽት»
ከሚለው ግርድፍ ፍቺው
በላይ ሰፍቶ «ኮራፕሽን»
ከሚለው
የእንግሊዘኛ ቃል ጋር
ተመሳሳይ ትርጉም
ይዟል፡፡
በእንግሊዘኛ መዝገበ
ቃላት ትርጉም
ኮራኘሽን ማለት ከጥሩ
ወይም ከጤነኛ ሁኔታ
መለወጥ፣ ከነበረበት
የጥራት ደረጃ
መቀነስ፣ የሞራል
ውድቀት፣ ዋጋ ማጣት፣
መቆሸሽ፣ በጉቦ
መለወጥ፣ ታማኝ
አለመሆን፣ በስህተት
ወይም በመጥፎነት
መበከል እንደሆነ
ተመልክቷል፡፡ በኢትዮጵያ
ወንጀል ሕግ
ከተዘረዘሩት የሙስና
ወንጀሎች ዋና
ዋናዎቹ፡- ·
በሥልጣን
ያለአግባብ
መገልገል፣ ·
ጉቦ
መቀበል፣ ·
የማይገባ
ጥቅም መቀበል፣ ·
የመንግሥት
ሥራን በማያመች
አኳኊን መምራት፣ ·
አደራ
በተሰጠው ዕቃ
ያለአግባብ ማዘዝ፣ ·
በሥራ
ተግባር ላይ የሚፈፀም
የመውሰድና የመሰወር
ወንጀል፣ ·
በሥልጣን
መነገድ፣ ·
በሕገወጥ
መንገድ መሰብሰብ
ወይም ማስረከብ፣ ·
ያለአግባብ
ጉዳይን ማጓተት፣ ·
ዋጋ
ያለውን ነገር
ያለክፍያ ወይም
ያለበቂ ክፍያ
ማግኘት፣ ·
ያለአግባብ
ፈቃድ መስጠትና
ማፅደቅ፣ ·
ምንጩ
ያልታወቀ ንብረትና
ገንዘብ ማካበት፣ ·
ጉቦ
መስጠት፣ ·
ዋጋ
ያለውን ነገር
ያለክፍያ ወይም
ያለበቂ ክፍያ
መስጠት፣ ·
ማቀባበል፣ ·
በሌላው
ሥልጣን መጠቀም፣ ·
በግል
ተሰሚነት መነገድ፣ ·
በምርጫ
ላይ የሚሰጥ መደለያ፣ ·
መንግሥታዊ
ወይም ወታደራዊ
ሰነዶችን አስመስሎ
ማዘጋጀት ወይም ወደ
ሐሰት መለወጥ፣ ·
በመንግሥት
ወይም በህዝባዊ
ድርጅት ንብረት ላይ
የተፈፀመ ከባድ
የእምነት ማጉደል
ወይም በመንግሥት
ባለሥልጣን ወይም ሹም
ወይም የሕዝብ
ባለአደራ ወይም
ተመራጭ የተፈፀመ
ከባድ የእምነት
ማጉደል፣ እንዲሁም
በሞግዚት ወይም
በንብረት ጠባቂ፣
በሂሳብ አጣሪ፣ በሕግ
ወይም በገንዘብ
አማካሪ፣ በወኪል፣
በጠበቃ፣ በንብረት
አስተዳዳሪ ወይም
በሥራው ወይም
በተሰጠው ኃላፊነት
ምክንያት ንብረት
በእጁ በገባ ማንኛውም
ሌላ ሰው የተፈፀመ
ከባድ የእምነት
ማጉደል፣ እና ·
በወንጀል
ድርጊት የተገኘን
ገንዘብ ወይም ንብረት
ሕጋዊ አስመስሎ
ማቅረብና በወንጀሉ
መርዳት ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ የሙስና ታሪካዊ አመጣጥን ስንመለከት በስልጣን ላይ ሆኖ በአንዳንድ ጥቅሞች ዙሪያ ለዘመድ ቅድሚያ መስጠት ሙስና እንደመፈፀም የማይቆጠርበት ወቅት እንደነበር ማስታወስ ይቻላል፡፡ በኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ኘሮግራም ጥናት ውስጥ እንደተመለከተው ከጥንት ጊዜ ጀምሮ አምባገነኖች እና ተከታዮቻቸው ከኢትዮጵያ ሕዝብ በገንዘብና በዓይነት ያለበቂ ምክንያት ምዝበራ ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡ የሚገርመው ነገር ግን መደለያ ሰጭው የሕብረተሰብ ክፍልም ሆነ ተቀባዩ ጉቦን እንደማበረታቻ እንጂ እንደ እኩይ ተግባር አይመለከቱትም ነበር፡፡ ከዚህ ባሻገር ዝምድናንና ትውውቅን መሠረት በማድረግ አድልኦ መፈፀም ሥልጣንን አለአግባብ እንደመጠቀም ፀያፍ ተግባር ሆኖ ከመቆጠር ይልቅ ጓደኛንና ዘመድን ለመርዳት እንደሚያስችል መልካም ተግባር ተደርጐ ሲወሰድ ነበር፡፡ አሁን ባለንበት ወቅት ሕብረተሰቡ በአንጻራዊ መልኩ በሙስና ችግር ዙሪያ ያለማመንታት በግልፅና በድፍረት ለመነጋገር ከዚያም አልፎ ሙስናን ለመከላከል ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ዝግጁነት እንደሚታይበት መገንዘብ ይቻላል፡፡ በርካታ የዘርፉ
ምሁራንና ባለሞያዎች
እንደሚስማሙበት
በአንድ ሕብረተሰብ
ውስጥ ለሙስና መከሰት
ምክንያት የሚሆኑ
በርካታ ጉዳዮች
ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሙስና በባህሪው
ውስብስብ ከመሆኑም
በላይ የተለያዩ መነሻ
ምክንያቶች ድምር
ውጤት ሲሆን
የሚያስከትለው
ማህበራዊና
ኢኮኖሚያዊ ቀውስም
ፈርጀ ብዙ ነው፡፡
በአገራችንም ሙስና
የሚከሰትባቸው
ምክንያቶች
በአብዛኛው ለችግሩ
በሌላው ዓለም
ከሚጠቀሱ ምክንያቶች
የተለዩ አይደሉም፡፡ በንጉሠነገሥቱም ሆነ በደርግ ዘመን ተንሰራፍቶ የቆየው ሙስና የመንግሥታቱን የአመራር ብቃት ጥያቄ ውስጥ ከማስገባቱ አልፎ የአስተዳደሩን መዋቅራዊ አደረጃጀት ያዳከመና የመንግሥትን የልማት ድርጅቶች ሀብት ለብዝበዛ ያጋለጠ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ የገበያ-መር ኢኮኖሚ ስርዓት ሚናና ምርታማነት እንዲዳከም፣ የአገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት አዝጋሚ እንዲሆን ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሯል፡፡ ይህም ድሕነት እንዲባባስና ለዝቅተኛው የሕብረተሰብ ክፍል ተገቢው ትኩረት እንዳይሰጥ፣ ኢንቨስትመንት እንዳይበረታታ፣ ማህበራዊ ቀውስ እንዲከሰትና በመጨረሻም መንግሥታቱ ከስልጣን እንዲወርዱ አንድ ምክንያት ሆኗል፡፡ በተመሣሣይ ሁኔታ ዛሬም ቢሆን አገራችን የጀመረችው የልማት እንቅስቃሴ እና የዲሞክራሲያዊ ሥርአት ግንባታ በአፋጣኝና በሚፈለገው ደረጃ ዕውን እንዳይሆን ሙስና የድርሻውን እያበረከተ ይገኛል፡፡ ከዚህ አንጻር መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳያገኝ ግብር ከመክፈል ነፃ ለመሆን የሚደረግ የሙስና ተግባር ተጠቃሽ ነው፡፡ ይህም በአገር አቀፍ ደረጃ ተፈፃሚ እየተደረገ የሚገኘውን የድሕነት ቅነሳ ኘሮግራም እየጐዳው እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ 2.5 ሙስና እንደተንሰራፋባቸው የሚታመኑ የአገልግሎት ዘርፎች
| |
|
|
|
|