|
ጠቅላላ
ክፍል
ሁለት
ስለዋስትናና
የፍርድ ቤት ስልጣን
ክፍል
ሶስት
ስለእግድ
ንኡስ
ክፍል
አንድ
የንብረት
ጠባቂ
ስለመሾም
ንኡስ
ክፍል
ሁለት
ስለማሸግና
የሀብት
ዝርዝር
ስለማዘጋጀት
ክፍል
አራት
ስለንብረት
አወራረስ
ሥነሥርአት
ክፍል
አምስት
ቅድመክስ
ዝግጅት
ክፍል
ሰባት
የሙስና
ድርጊትን
ስለሚጠቁሙ ሰዎች
ጥበቃ
ክፍል
ስምንት
ልዩ
ልዩ ድንጋጌዎች
አዋጅ
ቁ የተሻሻለው
የፀረ ሙስና ልዩ
የሥነሥርአት እና
የማስረጃ ህግ አዋጅ የሙስና
ወንጀል ትርጉምን፣
የክስ ሂደትና
የማስረጃ
ድንጋጌዎችን
ከወንጀል ህጉ ጋር
በተጣጣመ መልኩ
ማሻሻልና መደንገግ
በማስፈለጉ፣ በሙስና
ወንጀል ተጠርጥረው
የተያዙ ወይም
የተከሰሱ ሰዎች
በዋስትና
ስለሚለቀቁበት
ሁኔታ ዝርዝር
ድንጋጌ መደንገግ
በማስፈለጉ፣ በሙስና
ወንጀል የተጠረጠሩ
ሰዎችን ንብረት
ስለማገድ፣
ስለማስተዳደርና
ስለመውረስ
የተመለከቱትን
ድንጋጌዎች ማሻሻል
በማስፈለጉ፣ የጸረ
ሙስና ልዩ
ስነስርአትና
የማስረጃ ህግ
ድንጋጌዎችን
ከሌሎች ህጎች ጋር
በተጣጣመ ሁኔታ
ማስተካከልና
ማሻሻል
በማስፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀጽ 55/1 መሰረት የሚከተለው ታውጆአል፡፡
ክፍል
አንድ ጠቅላላ 1.
አጭር
ርእስ ይህ
አዋጅ <<የተሻሻለው
የጸረ ሙስና ልዩ
የሥነ ሥርአትና
የማስረጃ ህግ አዋጅ
ቁ
434/1997 ተብሎ
ሊጠቀስ ይችላል፡፡ 2.
ትርጓሜ የቃሉ
አገባብ ሌላ ትርጉም
የሚያሰጠው ካልሆነ
በስተቀር በዚህ
አዋጅ ውስጥ፣ 1. <<የሙስና
ወንጀል>>ማለት
በኢፌዴሪ የወንጀል
ሕግ የተመለከቱት
የሙስና ወንጀሎች
ናቸው፡፡ 2. <<በሙስና
ወንጀል የተገኘ
ንብረት>> ማለት
በተከሳሽ
ባለቤትነት ወይም
ይዞታ ስር የሚገኝ
በቀጥታም ሆነ
በተዘዋዋሪ መንገድ
በሙስና ወንጀል
የተገኘ ንብረት
ወይም ገንዘብ ሲሆን
ወንጀሉ ከተፈጸመ
በኋላ በቀጥታም ሆነ
በእጅ አዙር
ከተከሳሹ በስጦታ
የተሰጠ፣ 3. <<አግባብ
ያለው አካል>>ማለት
የሙስና ወንጀልን
ለመመርመር እና/
ወይም ለመክሰስ
ሥልጣን የተሰጠው
አካል ነው፡፡ 4. <<የእግድ
ትእዛዝ>> ማለት
ተከሳሽ በንብረቱ
ላይ ያለውን መብት
እንዳይጠቀምበት
የሚከለክል ትእዛዝ
ሲሆን በማናቸውም
መንገድ ለሌላ ሰው
ማስተላለፍን፣
የመጠቀም መብት
መስጠትንና
ማስወገድን
ይጨምራል፡፡ ይህ
አዋጅ በፌዴራልና
በክልል ሥልጣን ስር
በሚወድቁ የሙስና
ወንጀሎች
የምርመራና የክስ
ሂደት ተፈጻሚ
ይሆናል፡፡
ክፍል
ሁለት
ስለዋስትና
የፍርድ ቤት ስልጣን 4.
በሙስና
ወንጀል ተጠርጥረው
ስለተያዙ ሰዎች
በዋስትና የመፈታት
መብት
1.
በሙስና
ወንጀል የተያዘ ሰው
በዋስ እንዲለቀቅ
ለፍርድ ቤት
ማመልከት
ይችላል፡፡ ሆኖም
የተከሰሰበት
ወንጀል ከአስር
አመት በላይ
ሊያስቀጣ የሚችል
ከሆነ በዋስትና
መልቀቅ
አይቻልም፡፡ 2.
በሙስና
ወንጀል ተጠርጥሮ
የተያዘ ሰውን
መርማሪው ከዚህ
በታች በተመለከቱት
ሁኔታዎች የዋስትና
ወረቀት በማስፈረም
ወይም መያዣ
በማስያዝ ሊለቀው
ይችላል፤ h.
ተፈጸመ
የተባለው ወንጀል
ለመፈጸሙ
የሚያጠራጥር
ከሆነ፣ ወይም l.
የተያዘው
ሰው ወንጀሉን
ለመፈጸሙ
የሚያጠራጥር
ከሆነ፣ ወይም ሐ.
ተፈጸመ የተባለው
ወንጀል በጽኑ
እስራት የማያስቀጣ
ከሆነ 3.
በዚህ
አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 2 መሰረት
በዋስትና ወረቀት
ያልተለቀቀ ተከሳሽ
በዋስትና ወረቀት
እንዲለቀቅ ፍርድ
ቤትን ለመጠየቅ
ይችላል፡፡ 4.
በዚህ
አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 1
የተደነገገው
እንደተጠበቀ ሆኖ
በተከሳሹ ወይም
በዚህ አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 3 መሰረት
በተጠርጣሪው
የሚቀርበውን
በዋስትና ወረቀት
የመለቀቅ ጥያቄን
ፍርድ ቤቱ ከዚህ
በታች በተመለከቱት
ሁኔታዎች መፍቀድ
አይችልም፡፡ ሀ. ተጠርጣሪው ወይም ተከሳሹ በዋስትና ቢለቀቅ ይጠፋል ተብሎ የሚገመት ሲሆን ወይም፣ ለ.
ተጠርጣሪው ወይም
ተከሳሹ በዋስትና
ቢለቀቅ
ማስረጃዎችን
ያጠፋል ወይም ሌላ
ወንጀል ይፈጽማል
ተብሎ ሲገመት፣ 5.
የዋስትና
መብትን በማክበር
ወይም በመከልከል
በሚሰጥ ውሳኔ ላይ
ስለሚቀርብ ይግባኝ 1.
በዚህ
አዋጅ በአንቀጽ 4
በተመለከተው
መሰረት ፍርድ ቤት
ዋስትናን
በሚመለከት
በሚሰጠው ትእዛዝ
ላይ ይግባኝ ማቅረብ
ይቻላል፡፡ 2.
ይግባኙ
የቀረበው በዋስትና
መለቀቁን ወይም
የዋስትና ገንዘብ
መጠኑን በመቃወም
ከሆነ ጉዳዩ
በይግባኝ ታይቶ
እስኪወሰን ድረስ
የስር ፍርድ ቤት
ውሳኔው ሳይፈጸም
ይቆያል፡፡ 3.
ፍርድ ቤቱ በሙስና
ወንጀል
የተጠረጠረው ወይም
የተከሰሰው ሰው
በዋስትና
እንዲለቀቅ የወሰነ
እንደሆነ ፍርድ ቤቱ
ይግባኝ መጠየቁን
የሚያስረዳ የጽሁፍ
ማስረጃ ከይግባኝ
ሰሚው ፍርድ ቤት
ለማምጣት አግባብ
ነው ብሎ በሚወስነው
ጊዜ ውስጥ መርማሪው
ወይም አቃቤ ህጉ
ማስረጃውን ካላመጣ
በቀር አስፈላጊው
ስነስርአት ተሟልቶ
ተጠርጣሪው ወይም
ተከሳሹ እንዲለቀቅ
በውሳኔው ላይ
መግለጽ አለበት፡፡ ፍርድ
ቤቱ በዚህ አዋጅ
በአንቀጽ 4 ወይም 5
በተመለከተው
መሰረት የዋስትና
መብቱ በተከበረለት
ሰው ላይ ከዚህ በታች
ከተመለከቱት
አንዱን ወይም
ከአንድ በላይ ትእዛዞች
ሊሰጥ ይችላል፡፡ ሀ.
ከተወሰነ ክልል ውጭ
እንዳይንቀሳቀስ፣ ለ.
ማስረጃ ሊያጠፋ
በሚችልባቸው
የተወሰኑ ቦታዎች
እንዳይደርስ፣ ሐ.
በተወሰነ የጊዜ
ገደብ ውስጥ አግባብ
ላለው የምርመራ
አካል ሪፖርት
እንዲያደርግ፣ መ፣ወደውጭ
አገር እንዳይወጣ፣ 7. የሙስና ወንጀሎችን የማየት ስልጣን ስላለው ፍርድ ቤት 1.
አግባብ
ባለው ሕግ መሰረት
በፌዴራል ጠቅላይ
ፍርድ ቤት
የመጀመሪያ ደረጃ
የዳኝነት ስልጣን
እንዲታዩ
የተደነገጉት
እንደተጠበቁ ሆነው
ሌሎች በፌዴራል
መንግስት ስር
የሚወድቁ የሙስና
ወንጀሎችን
በሚመለከት
የፌዴራል ከፍተኛ
ፍርድ ቤት
የመጀመሪያ ደረጃ
የዳኝነት ስልጣን
አለው፡፡ 2.
አግባብ
ባለው ሕግ መሰረት
በክልል ጠቅላይ
ፍርድ ቤት
የመጀመሪያ ደረጃ
የዳኝነት ስልጣን
እንዲታዩ
የተደነገጉት ክሶች
እንደተጠበቁ
ሆነው ሌሎች በክልል
መንግስት ስር
የሚወድቁ የሙስና
ወንጀሎችን
በሚመለከት የክልል
ከፍተኛ ፍርድ ቤት
የመጀመሪያ ደረጃ
የዳኝነት ስልጣን
አለው፡፡ 3.
ከአዲስ
አበባ እና ከድሬዳዋ
አስተዳደሮች ጋር
በተያያዘ የሚፈጸሙ
የሙስና ወንጀሎችን
በመጀመሪያ ደረጃ
የማየት ስልጣን
እንደሁኔታው
አግባብ ባለው
የፌዴራል ፍርድ ቤት
የሚካሄድ
ይሆናል፡፡ 4 ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ የሚነሱ የመያዝ፣ የብርበራ፣ የቀነ ቀጠሮ፣ በማረፊያ ቤት የማቆየት፣ የዋስትና፣ የእግድ እንዲሁም ከምርመራ ጋር የተያያዙ ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች የሚታዩት የሙስና ወንጀሉን ክስ ለማየት ስልጣን በተሰጠው ፍርድ ቤት ይሆናል፡፡
ክፍል
ሶስት
ስለእግድ
8.
መርህ 1.
የዚህ
አዋጅ አንቀጽ 10
እንደተጠበቀ ሆኖ
ፍርድ ቤት በሙስና
ወንጀል የተገኘ
ማናቸውንም ንብረት
ለማገድ ይችላል፡፡ 2.
መርማሪ
ወይም ዐቃቤ ህግ
በሙስና ወንጀል
የተገኘ ንብረት
እንዲታገድ በቃለ
መሀላ በተደገፈ
መረጃ ለፍርድ ቤት
ማመልከት
ይችላል፡፡ 3.
ለእግድ
የሚቀርብ ማመልከቻ
የወንጀል ክስ
ከተመሰረተ በኋላ
ወይም የወንጀል ክሱ
ከመመስረቱ በፊት
ሊቀርብ ይችላል፡፡ 1.
በሙስና
ወንጀል የተገኘ
ለመሆኑ መረጃ
ባይቀርብም ምርመራ
በተጀመረበት ወይም
ክስ በቀረበበት
የሙስና ወንጀል
ተከሳሽ ያገኘው
የማይገባ ጥቅም
ወይም ያደረሰው
ጉዳት ለመኖሩ በቃለ
መሀላ ሲረጋገጥ
በወንጀሉ ተገኘ
ከተባለው የማይገባ
ጥቅም ወይም ደረሰ
ተብሎ ከሚገመተው
ጉዳት ጋር ተመጣጣኝ
የሆነ በተከሳሽ ስም
በባንክ የተቀመጠ
ገንዘብ ወይም
ንብረት ወይም
በተከሳሽ ስም ያለ
ንብረት
እንዳይሸጥ፣
እንዳይለወጥ፣
እንዳይተላለፍ፣
ታግዶ እንዲቆይ
በመርማሪ ወይም
በአቃቤ ህግ አቤቱታ
ሲቀርብ ፍርድ ቤት
የእግድ ትእዛዝ
ሊሰጥ ይችላል፡፡ 2.
በዚህ
አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 1 መሰረት
በሚሰጥ የእግድ
ትእዛዝ
የተጠርጣሪው
በታገደው ንብረቱ
የመጠቀም መብት
አይነካም፡፡ 10.
ስለማይታገዱ
ንብረቶች ለተከሳሹ
የእለት ኑሮ
አስፈላጊ የሆኑ
ንብረቶች በአንቀጽ 8
በተመለከተው
መሰረት የእግድ
ትእዛዝ
አያርፍባቸውም፣
የእግድ ትእዛዝ
ከማያርፍባቸው
ውስጥ በተለይ
የሚከተሉት
ይገኙበታል፣ 1.
ለተከሳሹና
ለቤተሰቡ የዕለት
አገልግሎት
የሚጠቅሙ ልብሶች፣
የምግብ ማብሰያ
የሆኑ የቤት
ቁሳቁስ፣የመኝታ
አልጋ፣ የአልጋ ልብሶችና
የብርድ ልብሶች፣ 2.
ለራሱና
ለቤተሰቡ ለዕለት
ኑሮ ጠቃሚ የሚሆን
ከሶስት ወር
ያልበለጠ ስንቅ፣ 3.
የተከሳሹንና
የቤተሰቡን የእለት
ኑሮ ለማሟላት
የሚያገለግሉ ቀላል
መሳሪያዎች፣ 4.
ተከሳሹና
ቤተሰቡ
የሚተዳደሩበት ሌላ
ንብረት የሌላቸው
ሲሆንና
የሚተዳደሩት
ከታገደው ንብረት
ከሚገኝ ገቢ ከሆነ
መሰረታዊ ፍላጎትን
ለማሟላት
ለተከሳሹና ለቤተሰቡ ፍርድ
ቤቱ በቂ ነው ብሎ
የሚገምተውን ያህል
ገቢ፣ 11.
የማመልከቻው
ይዘት 1.
የእግድ ትእዛዝ
እንዲሰጥ የሚቀርብ
በቃለመሀላ
የተደገፈ
ማመልከቻ፣
| ||