|
የተሻሻለው
የፌዴራል
የስነምግባርና
የጸረ ሙሰና ኮሚሽን
ማቋቋሚያ አዋጅ ክፍል
አንድ ጠቅላላ
ክፍል
ሁለት
ክፍል
ሶስት
ልዩ ልዩ
ድንጋጌዎች አዋጅ
ቁ የተሻሻለው
የፌዴራል
የስነምግባርና
የጸረ ሙሰና ኮሚሽን
ማቋቋሚያ አዋጅ የኢትዮጵያ
መንግስትና ሕዝቦች
ሙስና እና ብልሹ
አሠራር የአንድን
አገር ማህበራዊ፣
ኢኮኖሚያዊ እና
ፖለቲካዊ እድገት
የሚገታ ተግባር
መሆኑን የተገነዘቡ
በመሆናቸው፣ አገሪቱ
የተያያዘችውን
የእድገት ጎዳና እና
የዲሞክራሲያዊ
ሥርአት ግንባታ
ለማፋጠንና
ቀጣይነት ያለው
እንዲሆን ሙስናን
እና ብልሹ አሠራርን
በቁጥጥር ሥር ማዋል
አስፈላጊ በመሆኑ፣
ለዚህም ሙስናንና
ብልሹ አሰራርን
ለመሸከም
የማይፈልግ እና
ይህንኑ በብቃት
ለመዋጋት ዝግጁ
የሆነ ሕብረተሰብ
መፍጠር አስፈላጊ
በመሆኑ፣ ሙስናንና
ብልሹ አሰራርን
ለመመርመር፣
ለመክሰስ
ለመቆጣጠርና
ለመከላከል መልካም
ሥነ ምግባር
በኀብረተሰቡ
ውስጥ እንዲስፋፋ
በማድረግ ሙስናንና
ብልሹ አሠራርን
በብቃት መዋጋት
እንዲቻል፣
የኮሚሽኑን
አሰራርና
እንቅስቃሴ
የግልጽነትና
የተጠያቂነት
መርሆዎችን
በሚገልጽ መልኩ
እንዲሁም ኮሚሽኑ
ሀላፊነቱን በተሻለ
ብቃት እንዲወጣ
በሚያስችለው መልኩ የኮሚሽኑን
ማቋቋሚያ አዋጅ ለማሻሻል
በማስፈለጉ፣ የኮሚሽኑን
ስልጣንና ተግባር
ከኢትዮጵያ
ፌዴራላዊ
ዲሞክራሲያዊ
ሪፐብሊክ የወንጀል
ህግ ጋር በተጣጣመ
ሁኔታ ማሻሻል
በማስፈለጉ፣ ኮሚሽኑ
በከባድ የሙስና
ወንጀሎች ላይ
ትኩረት አድርጎ
እንዲንቀሳቀስ
ማድረግ አስፈላጊ
ሆኖ በመገኘቱ፣ ኮሚሽኑ
ከሌሎች አግባብነት
ካላቸው የምርመራና
የአቃቤ ህግ ተቋማት
ጋር ስለሚሰራበት
ሁኔታ ዝርዝር
ድንጋጌዎችን
መደንገግ
በማስፈለጉ፣ በሌሎችም
ግልጽነት
በሚያንሳቸው
አንዳንድ የአዋጁ
ድንጋጌዎች ላይ
ማሻሻያዎችን
ማድረግ
በማስፈለጉ፣ በኢትዮጵያ
ፌዴራላዊ
ዲሞክራሲያዊ
ሪፐብሊክ ህገ
መንግስት አንቀጽ 55/1/
መሰረት የሚከተለው
ታውጆአል፡፡ ክፍል
አንድ ጠቅላላ 1.
አጭር
ርእስ ይህ
አዋጅ <<የተሻሻለው
የፌዴራል
የስነምግባርና
የጸረ ሙስና ኮሚሽን
ማቋቋሚያ አዋጅ
ቁጥር 433/1997 >>
ተብሎ ሊጠቀስ
ይችላል፡፡ 2.
ትርጓሜ የቃሉ
አገባብ ሌላ ትርጉም
የሚያሰጠው ካልሆነ
በስተቀር በዚህ
አዋጅ ውስጥ፣ 1.
<<ኮሚሽን>>
ማለት የፌዴራል
የሥነ ምግባር እና
የጸረሙስና ኮሚሽን
ነው፡፡ 2.
<<ኮሚሽነር
እና ምክትል
ኮሚሽነር>> ማለት
እንደቅደም ተከተሉ
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር
ወይም ምክትል
ኮሚሽነር ነው፡፡ 3. <<የመንግስት
መስሪያ ቤት>> ማለት
ሙሉ በሙሉ ወይም
በከፊል በመንግስት
በጀት የሚተዳደር
እና የፌዴራል
መንግስቱ ስራዎች
የሚከናወኑበት
ማናቸውም መስሪያ
ቤት ነው፡፡ 4. <<የመንግስት
የልማት ድርጅት>>
ማለት የመንግስት
ባለቤትነት ድርሻ
በሙሉ ወይም በከፊል
ያለበት ማናቸውም
የፌዴራል መንግስት
የልማት ድርጅት
ወይም የአክሲዮን
ኩባንያ ነው፡፡ 5. <<የመንግስት
ባለሥልጣን>> ማለት
የህዝብ ተወካዮች
ምክር ቤትና
የፌዴሬሽን ምክር
ቤት አባሎች፣
ከሚኒስትር ደረጃ
በላይ የሆኑ
የፌዴራል መንግስት
ባለስልጣኖች፣
ሚኒስትሮች፣
ሚኒስትር
ዴኤታዎች፣ ምክትል
ሚኒስትሮች፣
ኮሚሽነሮች፣
ምክትል
ኮሚሽነሮች፣
የፌዴራል ጠቅላይ
ፍርድ ቤት ዳኞች፣
የብሄራዊ ክልላዊ
መንግስት ምክር ቤት
አባሎች፣ ከክልል
ቢሮ ሃላፊዎች በላይ
ያሉ ባለስልጣኖች፣
የክልል መንግስት
ቢሮ ሃላፊዎች፣
የክልል ጠቅላይ
ፍርድ ቤት ዳኞች፣
የአዲስ አበባ
መስተዳድርና
የድሬዳዋ
መስተዳድር የምክር
ቤት አባሎች፣
ከመስተዳድሮቹ ቢሮ
ሃላፊዎች በላይ ያሉ
ባለስልጣኖች፣
የመስተዳድሮቹ ቢሮ
ሃላፊዎች እና
በተመሳሳይ ደረጃ
ላይ የሚገኙ
የፌዴራል፣ የክልል
እንዲሁም የአዲስ
አበባና የድሬዳዋ
መስተዳድር
ባለስልጣኖችን
ይጨምራል፡፡ 6.
<<የመንግስት
ሠራተኛ>> ማለት በዚህ
አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 5 ውስጥ
ከተጠቀሱት ውጭ ያለ
በፌዴራል ወይም
በክልል ወይም
በአዲስ አበባ
መስተዳድር ወይም
በድሬዳዋ
መስተዳድር
የመንግስት መስሪያ
ቤት ወይም የልማት
ድርጅት ውስጥ
ተሹሞ፣ ተመድቦ፣
ተቀጥሮ፣ በህዝብ
ተመርጦ የሚሰራ ሰው
ነው፡፡ 7.
<<የሥነምግባር
አውታሮች>> ማለት
በመንግስት
አስተዳደር ውስጥ
ምግባረ ብልሹ
ባህርያትን
በከፍተኛ ደረጃ
ለመቀነስ እና ሙያዊ
ብቃትን እና መልካም
ሥነምግባርን
ለማበረታታት
የሚያገለግሉ
ዘዴዎች፣ አካላት፣
ሥርአቶች ወይም
አስፈላጊ ሁኔታዎች
እና የመሳሰሉት
ናቸው፡፡ 8.
<<ከባድ
የስነምግባር መጣስ>> ማለት ከስራ
ሊያሰናብት የሚችል
የሥነምግባር ጥፋት
ነው፡፡ 9.
<<ከባድ
የሙስና ወንጀል>>ማለት ሀ.
ከፍተኛ
ስትራቴጂያዊ
ጠቀሜታ ባላቸው
የመንግስት መስሪያ
ቤቶችና የመንግስት
የልማት ድርጅቶች
ላይ የሚፈጸሙ
ከፍተኛ የገንዘብ
መጠንን ያካተቱ
የሙስና ወንጀሎች
ወይም፣ ለ.
የመንግስት
ባለሥልጣንን
የሚመለከቱ የሙስና
ወንጀሎች ወይም፣ ሐ.
በአገር
ሉአላዊነት፣
ኢኮኖሚ፣ ጸጥታ
እንዲሁም
በሕብረተሰቡ ኑሮ
ላይ ከፍተኛ ጉዳት
የሚያደርሱ ወይም
ሊያደርሱ የሚችሉ
የሙስና ወንጀሎች
ናቸው፡፡ 10.
<<የባንክ ሂሳብ>>
ማለት በባንክ
የተቀመጠ ገንዘብ፣
ወርቅና የመሳሰሉት
ውድ እቃዎች
እንዲሁም አንድ
ደንበኛ ከባንኩ ጋር
የሚያደርጋቸውን
ማናቸውንም
ግንኙነቶች/
T‰N²K>ñC
/ የሚያጠቃልል
ነው፡፡ 11.<<ሰው>>
ማለት የተፈጥሮ ሰው
ወይም በሕግ
የሰውነት መብት
የተሰጠው አካል
ነው፡፡ ክፍል
ሁለት
ስለኮሚሽኑ
መቋቋም እና
ሥልጣንና ተግባር 3.
የኮሚሽኑ
መቋቋም 1.
የፌዴራል
የሥነምግባር እና
የጸረ ሙስና ኮሚሽን/
ከዚህ በኋላ ኮሚሽኑ
እየተባለ የሚጠራ/
ራሱን የቻለ
የፌዴራል መንግስት
መሥሪያ ቤት ሆኖ
በዚህ አዋጅ መሰረት
ተቋቁሟል፡፡ 2.
የኮሚሽኑ
ተጠሪነት ለጠቅላይ
ሚኒስትሩ
ይሆናል፡፡ በዚህ አዋጅ በአንቀጽ 3 ንኡስ አንቀጽ 2 የተደነገገው ቢኖርም ኮሚሽኑ በሚመረምራቸው ወይም ክስ በሚመሰርትባቸው ወይም ክስ በመሰረተባቸው ጉዳዮች ላይ ከማንኛውም ሰው ወይም አካል ጣልቃ ገብነትና አመራር ነጻ ነው፡፡ 5.
ዋና
መስሪያ ቤት የኮሚሽኑ ዋና መስሪያ ቤት አዲስ አበባ ይሆናል፡፡ ሆኖም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በየክልሉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶችን ሊያቋቁም ይችላል፡፡ 6.
የኮሚሽኑ
ዓላማዎች ኮሚሽኑ
የሚከተሉት
ዓላማዎች
ይኖሩታል፡፡ 1.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር የሥነ
ምግባር እና የጸረ
ሙስና ትምህርቶችን
በማስፋፋት የነቃ
እና ሙስናን ሊሸከም
የማይችል
ሕብረተሰብ
እንዲፈጠር ጥረት
ማድረግ፣ 2.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር የሙስና
ወንጀልን እና ብልሹ
አሠራርን
መከላከል፣ 3.
የሙስና
ወንጀልን እና ብልሹ
አሠራርን ማጋለጥ፣
መመርመር እና
መክሰስ፣ ኮሚሽኑ
የሚከተሉት
ሥልጣንና ተግባራት
ይኖሩታል፣ 1.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር
ስለሙስና ጎጂነት
የህዝቡ ንቃተ ህሊና
እንዲጎለብት
በማስተማር እና
መልካም ሥነምግባር
በሕዝብ አገልግሎት
እና በኀብረተሰቡ
ውስጥ እንዲስፋፋ
በማድረግ ሙስናንና
ብልሹ አሰራርን
መዋጋት፣ 2.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር
በመንግስት መ/ቤቶች
እና በመንግስት
ልማት ድርጅቶች
ውስጥ ለሙስናና
ለብልሹ አሰራር
የተጋለጡና ሊጋለጡ
የሚችሉ የአሰራር
ሥርአቶችን
በማጥናት ወይም
እንዲጠኑ በማድረግ
እንዲሻሻሉ
ማማከርና ማሳሰብ፣
የአሰራር ስርአቶቹ
የተሻሻሉ
መሆናቸውን
መከታተል እና
አስፈላጊ ሆኖ
ሲገኝም ተገቢ የሆነው
እርምጃ እንዲወሰድ
ወይም ውሳኔ
እንዲሰጥ አግባብ
ላለው አካል
በማሳወቅ ወይም
በማሳሰብ ሙስናን
የመከላከል፣
በሌሎች ሰዎች
ሲጠየቅ ተመሳሳይ
ምክርና ድጋፍ
የመስጠት፣ 3.
በመንግስት
መ/ቤቶች እና
በመንግስት ልማት
ድርጅቶች ውስጥ
ከባድ የሥነምግባር
መጣስ ስለመፈጸሙ
ጥቆማ ሲደርሰው
ወይም በቂ ጥርጣሬ
ሲኖረው የማጣራት
ወይም እንዲጣራ
የማድረግ እና
ተገቢው እርምጃ
እንዲወሰድ
የመከታተል፣ 4.
በመንግስት
መ/ቤቶች ወይም
በመንግስት ልማት
ድርጅቶች ወይም
ፌዴራል መንግስቱ
ለክልሎች ከሚሰጠው
ድጎማ ጋር በተያያዘ
በክልል መ/ቤቶች
በወንጀል ህግ እና
በሌሎች ሕጎች ውስጥ
የተመለከቱት
የሙስና ወንጀሎች
በመንግስት
ሰራተኞች ወይም
ባለስልጣኖች ወይም
በሌሎች ሰዎች
ስለመፈጸማቸው
ጥቆማ ሲደርሰው
ወይም በቂ ጥርጣሬ
ሲኖረው
የመመርመርና
የመክሰስ ወይም
እንዲመረመር ወይም
እንዲከሰስ
የማድረግ፣ 5.
ከሙስና
ወንጀል ጋር
በተያያዘ በቂ
ጥርጣሬ ሲኖረው በማናቸውም
ባንክ የሚገኝ
የተጠርጣሪዎች
የባንክ ሂሳብ
በኮሚሽነሩ ትእዛዝ
እንዲመረመር
የማድረግ፣ መረጃ
የማግኘት እና
አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ
በፍርድ ቤት ትእዛዝ
እንዲከበር
የማድረግ፣ 6.
ከሙስና
ወንጀል ጋር
በተያያዘ በምርመራ
ላይ ያሉ ሰዎች ሀብት
በፍርድ ቤት ትእዛዝ
እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ፣ በሙስና
ወንጀል የተገኘ
ለመሆኑ
የተረጋገጠን ወይም
በሙስና ወንጀሉ
ከተገኘው ጥቅም ጋር
ተመጣጣኝ የሆነ
ማናቸውንም ንብረት
ወይም ሀብት በፍርድ
ቤት ትእዛዝ
እንዲወረስና
በሐራጅ ተሸጦ ወይም
ሳይሸጥ ለመንግስት
ገቢ እንዲሆን
የማድረግ፣ 7.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር በህግ
በሚደነገገው
መሰረት የመንግስት
ባለስልጣኖችን እና
በህግ ሀብታቸውንና
የገንዘብ
ጥቅማቸውን
እንዲያስመዘግቡ
ግዴታ ያለባቸውን
የመንግስት
ሰራተኞች ሀብትና
የገንዘብ ጥቅሞች
መዝግቦ የመያዝ
ወይም ተመዝግበው
እንዲያዙ
የማድረግ፣ 8.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር ለሙስና
ወንጀል ጠቋሚዎችና
ምስክሮች የአካልና
የሥራ ዋስትና ጥበቃ
የሚሰጥበትን ሁኔታ
ማመቻቸት፣ በህግ
በሚወሰን መሰረት
ጥበቃ የመስጠት፣ 9.
ሙስናን
በመታገል እና
በመከላከል ረገድ
ጥሩ ውጤት ያስገኙ
ሰዎችን እና መ/ቤቶችን
አወዳድሮ ለሽልማት
የሚበቁበትን
ሥርአትና መለኪያ
የመዘርጋት፣
ሲጸድቅም ተግባራዊ
የማድረግ፣ 10.
የሕግ
አውጪና የዳኘነት
አካላትን ሳይጨምር
ለመንግስት መስሪያ
ቤቶችና ለመንግስት የልማት ድርጅቶች
የሚያገለግሉ
የሥነምግባር
ደንቦች
መዘጋጀታቸውን
ማረጋገጥ ወይም
ማዘጋጀት እና
አፈጻጸማቸውን
የመከታተል፣ ከሕግ
አውጭ እና ከዳኝነት
አካላት ጥያቄ
ሲቀርብለት
በሥነምግባር ደንብ
አዘገጃጀት ረገድ
ምክር የመስጠት፣ 11.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር
የሥነምግባር
አውታሮችን
የማስተባበር፣ 12.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር የሥነምግባርን እና
ሙስናን በተመለከተ
ጥናትና ምርምር
የማድረግ እና
ተመሳሳይ ሥራዎችን
የመደገፍ፣
የኮሚሽኑን
አላማዎች ለማራመድ
የሚረዱ ሪፖርቶችን
እና ቴክኒካዊ
ጥናቶችን አሳትሞ
የማሰራጨት፣ 13.
አግባብነት
ካላቸው አካላት ጋር
በመተባበር የጸረ
ሙስና ህጎች
መከበራቸውን
የመከታተል እና
የማረጋገጥ
ስለአፈጻጸማቸው
የምክር አገልግሎት
የመስጠት፣ 14.
በመንግስት
መስሪያ ቤቶችና
የልማት ድርጅቶች
ውስጥ የስነምግባር
መከታተያ ክፍሎች
እንዲቋቋም ድጋፍ
የማድረግ፣ 15.
ለክልሎች
አስፈላጊውን
የምክርና የድጋፍ
አገልግሎት
የመስጠት፣ 16.
ተመሳሳይ
አላማ ካላቸው
አገራዊ፣
አህጉራዊና ዓለም
አቀፋዊ አካላት ጋር
ግንኙነትና ትብብር
የመፍጠር፣ 17.
የንብረት
ባለቤት የመሆን፣
ውል የመዋዋል፣
በራሱ ስም
የመክሰስና
የመከሰስ፣ 18.
በሕግ
የሚሰጡትን እና
ዓላማውን ከግብ
ለማድረስ የሚረዱ
ሌሎች ተግባራትን
የማከናወን፡፡ 8.
በሌሎች
አካላት ስለሚደረግ
የሙስና ወንጀል
ምርመራ 1.
ኮሚሽኑ
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 7
ንኡስ አንቀጽ 4
ከተሰጠው ሥልጣን
ውስጥ ከባድ ያልሆነ
የሙስና ወንጀልን
የመመርመር ጠቅላላ
ውክልና በሙሉ ወይም
በከፊል
እንደሁኔታው
ለፌዴራል ወይም
ለክልል የወንጀል
መርማሪ አካላት
ሊሰጥ ይችላል፡፡ 2.
በዚህ
አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 1 መሰረት
ውክልና ያልተሰጠው
ማንኛውም ወንጀልን
ለመመርመር ስልጣን
ያለው የፌዴራል
ወይም የክልል
መንግስታዊ አካል
በዚህ አዋጅ
በአንቀጽ 7 ንኡስ
አንቀጽ 4 በኮሚሽኑ
የስልጣን ክልል ስር
የሚወድቅ የሙስና
ወንጀል ለመፈጸሙ
ጥቆማ ሲደርሰው
ወይም በቂ ጥርጣሬ
ሲኖረው ምርመራ
መጀመር
ይኖርበታል፡፡
ሆኖም ስለተጀመረው
ምርመራ ለኮሚሽኑ
ሳይዘገይ
ያሳውቃል፡፡ 3.
በዚህ
አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 2
በተመለከተው
መሰረት ኮሚሽኑ
ሪፖርት ሲደርሰው ሀ.
ጉዳዩን እራሱ ወስዶ
ይመረምራል ወይም ለ.
ከባድ የሙስና
ወንጀልን ጨምሮ
ምርመራው ሪፖርት
ባደረገው የምርመራ
አካል ወይም በሌላ
አካል እንዲከናወን
ሊያደርግ
ይችላል፡፡ ዝርዝሩ
ኮሚሽኑ በሚያወጣው
መመሪያ
ይወሰናል፡፡ 4.
ኮሚሽኑ
በዚህ አንቀጽ ንኡስ
አንቀጽ 2 መሰረት
በሚቀርብለት
ሪፖርት መሰረት
መልስ ሳይሰጥ ከቀረ
ምርመራውን
የጀመረው አካል
የተጀመረውን
ምርመራ በማጠናቀቅ
የምርመራ ፋይሉን
ክስ ለመመስረት
ስልጣን ላለው አካል
ያስተላልፋል፡፡ 5.
ኮሚሽኑ
በቀጥታ በሚደርሰው
ጥቆማ ወይም በሌላ
መልኩ በሚያገኘው
መረጃ መሰረት
የጀመራቸውን
የሙስና ወንጀል
ምርመራዎች በሌሎች
የምርመራ አካላት
እንዲመረመር
ሊያደርግ
ይችላል፡፡
ማንኛውም በዚህ
ንኡስ አንቀጽ
መሰረት የምርመራ
ፋይል የተላለፈለት
አካል ምርመራውን
ማከናወን
ይኖርበታል፡፡ 6.
በዚህ
አንቀጽ ከንኡስ
አንቀጽ 2 እስከ 5
በተመለከተው
መሰረት በሌሎች
የምርመራ አካላት
ስለሚከናወኑ
የሙስና ወንጀል
ምርመራዎች ሪፖርት
ስለሚደረግበት
ሁኔታ ኮሚሽኑ
ዝርዝር መመሪያ
ያወጣል፣
ለሚመለከታቸው
የምርመራ አካላት
ያሳውቃል፡፡ 9. በሌሎች የፍትህ አካላት የሙስና ወንጀል ክስ ስለመመስረት 1.
ኮሚሽኑ
ከአቃቤ ህግነት
ስልጣኑ ውስጥ
አግባብነት ላለው
የፌዴራል ወይም
የክልል አቃቤ ህግ
ወይም
የስነምግባርና
የጸረ ሙስና ተቋም
በሙሉ ወይም በከፊል
ውክልና ሊሰጥ
ይችላል፡፡ 2.
ከፌዴራል መንግስት
ለክልል መንግስታት
ከተሰጠ የበጀት
ድጎማ ጋር በተያያዘ
የክልል
የስነምግባርና ጸረ
ሙስና ተቋም ወይም
ስልጣን ያለው አቃቤ
ህግ ክስ መመስረት
ይችላል፡፡ ሆኖም
ኮሚሽኑ አስፈላጊ
ሆኖ ካገኘው
በማንኛውም ጊዜ
የክልሉን
የስነምግባርና ጸረ
ሙስና ተቋም ወይም
አቃቤ ህግ በመተካት
በክርክሩ ውስጥ
ሊገባ ይችላል፡፡ 10.
የኮሚሽኑ
አቋም ኮሚሽኑ፣ 1. በጠቅላይ ሚኒስትሩ ǜ | ||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||